Telegram Group & Telegram Channel
"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ"
【መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፳፫】
°✞°°°°°°°°°°°°°°°✥°°°°°°°°°°°°°°°°†°(#ነገረ_ከተራ)

«አሁንስ አበዛችሁት!» ይላሉ ዳታንና አቤሮን እንዲሁም ሐሳባቸውን የገዙ ቆሬና ልጆቹ【ዘኁ. ፲፮፥፫】 የዛሬዎቹን ‘ሁላችን የሀዲስ ኪዳን ካህናት ነን’ ባዮቹን መስለውና በሙሴ ፊት በመቆም

‘አሮንን ብቻ ማን ካህን አደረገው እኛስ ካህን ለመሆን ምን ያንሰናል?’ እያሉ

ጨምረው እንዲህ ይላሉ «ማኅበሩ ሁላቸውም እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸው» ወይ መመሳሰል እንዴት ይደንቃል! ራሳችሁን ቅዱሳን ቅዱሳን እያላችሁ የምትጠራሩና የምትንጠራሩ ደቂቀ ዳታን ውሉደ አቤሮን ኧረ አድቡ። በእግዚአብሔር ምርጫ ላይ አፍ የሚከፍቱትን መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች እኮ!

ዛሬ በውሥጥ በውጪ የቸገረ ነገር የሆነው እንዲህ ዐይነቱ ግብረ ዕቡያን ነው።

⇄ በውሥጥ «አሁንስ እጅግ አበዛችሁት!» እያሉ ከመንበረ ፓትርያርክ ውጪ <መንበረ ሃሮ ዘኦሮሚያ> እና <መንበረ አክሱም ዘትግራይ> እያሉ ራሳቸውን በየሰፈራቸው የቀባቡና የተቀባቡ በሥልጣነ መለኮት ላይ የተሳለቁ የጥምቀት ማግሥት ጉዶች አየን።

⇆ በውጭ ክርስቲያን ነን የሚሉ ደፍረው ራሳቸውን ቅዱስ እያሉ የጠሩ ባለክህነት ለመሆንስ ማን ከልክሎን ብለው በዘፈቀደ የሚሿሿሙ!

ውጤቱ ምን ነበር?
ሙሴ ለቆሬ ልጆች «እጅግ ያበዛችሁትስ እናንተ ናችሁ» 【ዘኁ ፲፮፥፯】እኛ አልከለከልናችሁ ተፈቀደልን ካላችሁ በሉ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ አግኙት አላቸው ፤ እነ ሙሴ እነ አሮነን ተሰበሰቡ በጉዳዩ ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ ከዚያ ጠሯቸው « አንመጣም! በእኛ ላይ ራስህን አለቃ ታደርጋለህ?" አሉ 【ዘኁ ፲፮፥፲፪/፲፫】

አወይ መመሳሰላችን እናንተዬ። ዛሬም አስኬማውን ከማጀት እንደተገኘ የቤታቸው ድስት አጥልቀው በየጎሳቸው የሚሮጡ ሲጠሩ እምቢኝ ብለው በየጓዳው የሚቀላውጡ አቤሮናውያን አየን።

ብቻ ተክህነናል ያሉቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው 250ዎቹን አጣኝ ነን ባዮች ደቂቀ ቆሬና 14,700 ተከታዮቻቸውን መቅሰፍት እሳት ከሰማይ ወርዳ በልታቸዋለች።

ያን ጊዜ ካህኑ አሮን ወደቀሩት ሕያዋን መቅሰፍት እሳቱ እዳይሻገር ከሙታኑ መንደር እንዲቀር በመካከል ቆሞ ያጥን ጀመር ያን ጊዜ #ከተራ_ሆነ። ‘ወበማዕከሎሙ ቀዊሞ ከተረ መዓተ’ ይለዋል።
“በሙታንና በሕያዋን መካከል ቆመ፤ መቅሠፍቱም ተከለከለ።” 【ዘኁ ፲፮፥፵፰】

ጠቢቡ ሰሎሞን ላለፈው የካህኑ አሮንን ለሚመጣው የሊቀ ካህናቱ የክርሰቶስን አይቶ ነገሩን እንዲህ እያለ በጥበብ መጽሐፍ ያስተምርበታል።

"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ
አኮ በኃይለ ሥጋ ወኢበግብረ ንዋየ ሐቅል አላ በቃለ ዚአከ በዘአዘከረ ሎቱ መሐላ አበው ወኪዳኖሙ ☞ በሥጋዊ ኃይልና ለጦርነት በሚሆን መሣርያ አይደለም በራስህ ቃል ለቅዱሳን አበው የማለውን መሐላ የገባላቸውን ቃልኪዳን አስቦ በሞታንና በሕያዋን መካከል ቆሞ መዓቱን ከተረ/አቆመ " 【ጥበ. ፲፰፥፳፫】

የቀደመው አሮን በሙታኑና በሕያዋኑ መካከል ቆሞ "ተዘከር አብርሃምሃ ወይስሐቅሃ ወያዕቆብሃ ዘመሐልከ በርእስከ ☞ ለአብርሃም ለይስሐቅና ለያዕቆብ በራስህ የማልከውን መሐላ አስብ" እያለ መዓቱን ከለከለ መቅሰፍቱን አቆመ። ከተራ ይለዋል እንዲህ ያለውን የመዓቱን መቆም የምሕረቱን መምጣት!

ቀዳማዊና ደኃራዊ ፊተኛውና ኋላኛው ዘልዓለማዊው የሐዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህናት ክርስቶስ "የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል" ተብሎ በበረኛው በዮሐንስ መጥምቅ የተመሰከረለት የነፍሳችን እረኛ በጥምቀቱ በኦሪታውያኑ ምውታንና በሀዲስ ኪዳኑ ሕያዋን መካከል ቆሞ በቁጣው እሳት በአዳም ዘር ላይ የነደደውን መርገማችንን ደምስሶ መዓቱን በምሕረት መልሶ ባርነቱን አቆመልን። ይህ #በጥምቀቱ_የተገኘ_ከተራ ነው።

① የበጉ እናት የሊቀ ካህናቱ ወላዲት እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለዚህ ከተራ መዓቱን አርቆ ምሕረቱን ልኮ ድኅነቱ ስለተሠጠበት ምሥጢር ይህን ትሰብክልናለች
“እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ”
【ሉቃስ ፩፥፸፪-፸፫】

② ይህን ከተራ ከድግል እመቤታችን ቀጥላ የሰበከችው አንቀጽ የተባለች ዮርዳኖስ ናት፤ ራሷ ቆማና ሸሽታ ከተራውን በተግባር እየመሰከረች
“አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?” 【መዝ ፻፲፬፥፭】

③ በጥምቀቱ የተፈጸመልንን የነገረ ከተራውን ምስክርነት ዐጻዌ ኆኅት፣ ጺያሔ ፍኖት የተባለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ለሦስተኛ ጊዜ አጽንቶታል “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ (የሚከትር) የእግዚአብሔር በግ።”
【ዮሐ ፩፥፳፱】

ከተራ የሚለው ቃል በቁሙ ከመነሻው ከተረ ብሎ ዘጋ አቆመ አገደ ከለከለ ማለት ነው በቀረበ አውድ ደግሞ ከበበ ዐጠረ ዙሪያውን ያዘ ማለትም ይሆናል በተከበበ ገንዳ በታጠረ ሥፍራ ጥምቀቱን ከከተራ አንስተን ማክበራችን ለዚሁ ነው።

ከወንጌሉ ክፍል ለማጠቃለያ የሚሆነንን አንድ ምንባብ እናንሳና ነገረ ከተራችንን እንቋጭ

"እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና"
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ከቁጥር ፩―፲

በበሩ የማይገቡ «ቅዱሳን ነን ካህናት ነን» ባዮች ብዙ ወንበዴዎች አሉ። እነዚህ መዓት የማይከተርላቸው እሳተ ሲዖል የሚበላቸው የገሃነም አፍ የሚውጣቸው ናቸው። ሊቃውንቱ በሩን ወደእርሱ መግባትን ያገኘንባት እረኛችን ክርስቶስ እኛን ያገኘባት የምሥጢራቱ መግቢያ ቅድስት ጥምቀት ናት ይሉናል።
☞ ኖላዊ ኄር ዘይቤ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውእቱ (‹‹ቸር ጠባቂ›› ያለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።)
☞ ወአንቀጽኒ ፈለገ ዮርዳኖስ ውእቱ (‹‹በርም›› የዮርዳኖስ ወንዝ(ጥምቀት) ነው።)
☞ ወዐጻዊሰ ዮሐንስ መጥምቅ ውእቱ (‹‹በረኛውም›› ዮሐንስ መጥምቅ ነው፡፡)
☞ ወዐጸድ መንግሥተ ሰማያት ይእቲ ( ‹‹ስፍራም›› መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ )

አበው ሲተርቱ «ባጤ ሞት የተከተረ በስለት የተመተረ አንድ ነው» ይላሉ። ለእኛ የሕይወታችን ዐጤ የነፍሳችን ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ከሥፍራችን እንዳንታጣ ከቤቱ እንዳንወጣ በሞት ሳይሆን በሕይወት እንዲከትረን ከዘልዓለማዊ ዐጸድ ከሰማይ ቤቱ እንዳንጎድልና በፍርዱ ሠይፍ እንዳንመተር ከሥላሴ ልጅነታችን ከተዋህዶ ሃይማኖታችን አያናውጸን።

✍️ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ደቡብ ሱዳን ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን የተጻፈ



tg-me.com/orthodox1/13083
Create:
Last Update:

"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ"
【መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፳፫】
°✞°°°°°°°°°°°°°°°✥°°°°°°°°°°°°°°°°†°(#ነገረ_ከተራ)

«አሁንስ አበዛችሁት!» ይላሉ ዳታንና አቤሮን እንዲሁም ሐሳባቸውን የገዙ ቆሬና ልጆቹ【ዘኁ. ፲፮፥፫】 የዛሬዎቹን ‘ሁላችን የሀዲስ ኪዳን ካህናት ነን’ ባዮቹን መስለውና በሙሴ ፊት በመቆም

‘አሮንን ብቻ ማን ካህን አደረገው እኛስ ካህን ለመሆን ምን ያንሰናል?’ እያሉ

ጨምረው እንዲህ ይላሉ «ማኅበሩ ሁላቸውም እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸው» ወይ መመሳሰል እንዴት ይደንቃል! ራሳችሁን ቅዱሳን ቅዱሳን እያላችሁ የምትጠራሩና የምትንጠራሩ ደቂቀ ዳታን ውሉደ አቤሮን ኧረ አድቡ። በእግዚአብሔር ምርጫ ላይ አፍ የሚከፍቱትን መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች እኮ!

ዛሬ በውሥጥ በውጪ የቸገረ ነገር የሆነው እንዲህ ዐይነቱ ግብረ ዕቡያን ነው።

⇄ በውሥጥ «አሁንስ እጅግ አበዛችሁት!» እያሉ ከመንበረ ፓትርያርክ ውጪ <መንበረ ሃሮ ዘኦሮሚያ> እና <መንበረ አክሱም ዘትግራይ> እያሉ ራሳቸውን በየሰፈራቸው የቀባቡና የተቀባቡ በሥልጣነ መለኮት ላይ የተሳለቁ የጥምቀት ማግሥት ጉዶች አየን።

⇆ በውጭ ክርስቲያን ነን የሚሉ ደፍረው ራሳቸውን ቅዱስ እያሉ የጠሩ ባለክህነት ለመሆንስ ማን ከልክሎን ብለው በዘፈቀደ የሚሿሿሙ!

ውጤቱ ምን ነበር?
ሙሴ ለቆሬ ልጆች «እጅግ ያበዛችሁትስ እናንተ ናችሁ» 【ዘኁ ፲፮፥፯】እኛ አልከለከልናችሁ ተፈቀደልን ካላችሁ በሉ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ አግኙት አላቸው ፤ እነ ሙሴ እነ አሮነን ተሰበሰቡ በጉዳዩ ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ ከዚያ ጠሯቸው « አንመጣም! በእኛ ላይ ራስህን አለቃ ታደርጋለህ?" አሉ 【ዘኁ ፲፮፥፲፪/፲፫】

አወይ መመሳሰላችን እናንተዬ። ዛሬም አስኬማውን ከማጀት እንደተገኘ የቤታቸው ድስት አጥልቀው በየጎሳቸው የሚሮጡ ሲጠሩ እምቢኝ ብለው በየጓዳው የሚቀላውጡ አቤሮናውያን አየን።

ብቻ ተክህነናል ያሉቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው 250ዎቹን አጣኝ ነን ባዮች ደቂቀ ቆሬና 14,700 ተከታዮቻቸውን መቅሰፍት እሳት ከሰማይ ወርዳ በልታቸዋለች።

ያን ጊዜ ካህኑ አሮን ወደቀሩት ሕያዋን መቅሰፍት እሳቱ እዳይሻገር ከሙታኑ መንደር እንዲቀር በመካከል ቆሞ ያጥን ጀመር ያን ጊዜ #ከተራ_ሆነ። ‘ወበማዕከሎሙ ቀዊሞ ከተረ መዓተ’ ይለዋል።
“በሙታንና በሕያዋን መካከል ቆመ፤ መቅሠፍቱም ተከለከለ።” 【ዘኁ ፲፮፥፵፰】

ጠቢቡ ሰሎሞን ላለፈው የካህኑ አሮንን ለሚመጣው የሊቀ ካህናቱ የክርሰቶስን አይቶ ነገሩን እንዲህ እያለ በጥበብ መጽሐፍ ያስተምርበታል።

"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ
አኮ በኃይለ ሥጋ ወኢበግብረ ንዋየ ሐቅል አላ በቃለ ዚአከ በዘአዘከረ ሎቱ መሐላ አበው ወኪዳኖሙ ☞ በሥጋዊ ኃይልና ለጦርነት በሚሆን መሣርያ አይደለም በራስህ ቃል ለቅዱሳን አበው የማለውን መሐላ የገባላቸውን ቃልኪዳን አስቦ በሞታንና በሕያዋን መካከል ቆሞ መዓቱን ከተረ/አቆመ " 【ጥበ. ፲፰፥፳፫】

የቀደመው አሮን በሙታኑና በሕያዋኑ መካከል ቆሞ "ተዘከር አብርሃምሃ ወይስሐቅሃ ወያዕቆብሃ ዘመሐልከ በርእስከ ☞ ለአብርሃም ለይስሐቅና ለያዕቆብ በራስህ የማልከውን መሐላ አስብ" እያለ መዓቱን ከለከለ መቅሰፍቱን አቆመ። ከተራ ይለዋል እንዲህ ያለውን የመዓቱን መቆም የምሕረቱን መምጣት!

ቀዳማዊና ደኃራዊ ፊተኛውና ኋላኛው ዘልዓለማዊው የሐዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህናት ክርስቶስ "የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል" ተብሎ በበረኛው በዮሐንስ መጥምቅ የተመሰከረለት የነፍሳችን እረኛ በጥምቀቱ በኦሪታውያኑ ምውታንና በሀዲስ ኪዳኑ ሕያዋን መካከል ቆሞ በቁጣው እሳት በአዳም ዘር ላይ የነደደውን መርገማችንን ደምስሶ መዓቱን በምሕረት መልሶ ባርነቱን አቆመልን። ይህ #በጥምቀቱ_የተገኘ_ከተራ ነው።

① የበጉ እናት የሊቀ ካህናቱ ወላዲት እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለዚህ ከተራ መዓቱን አርቆ ምሕረቱን ልኮ ድኅነቱ ስለተሠጠበት ምሥጢር ይህን ትሰብክልናለች
“እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ”
【ሉቃስ ፩፥፸፪-፸፫】

② ይህን ከተራ ከድግል እመቤታችን ቀጥላ የሰበከችው አንቀጽ የተባለች ዮርዳኖስ ናት፤ ራሷ ቆማና ሸሽታ ከተራውን በተግባር እየመሰከረች
“አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?” 【መዝ ፻፲፬፥፭】

③ በጥምቀቱ የተፈጸመልንን የነገረ ከተራውን ምስክርነት ዐጻዌ ኆኅት፣ ጺያሔ ፍኖት የተባለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ለሦስተኛ ጊዜ አጽንቶታል “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ (የሚከትር) የእግዚአብሔር በግ።”
【ዮሐ ፩፥፳፱】

ከተራ የሚለው ቃል በቁሙ ከመነሻው ከተረ ብሎ ዘጋ አቆመ አገደ ከለከለ ማለት ነው በቀረበ አውድ ደግሞ ከበበ ዐጠረ ዙሪያውን ያዘ ማለትም ይሆናል በተከበበ ገንዳ በታጠረ ሥፍራ ጥምቀቱን ከከተራ አንስተን ማክበራችን ለዚሁ ነው።

ከወንጌሉ ክፍል ለማጠቃለያ የሚሆነንን አንድ ምንባብ እናንሳና ነገረ ከተራችንን እንቋጭ

"እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና"
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ከቁጥር ፩―፲

በበሩ የማይገቡ «ቅዱሳን ነን ካህናት ነን» ባዮች ብዙ ወንበዴዎች አሉ። እነዚህ መዓት የማይከተርላቸው እሳተ ሲዖል የሚበላቸው የገሃነም አፍ የሚውጣቸው ናቸው። ሊቃውንቱ በሩን ወደእርሱ መግባትን ያገኘንባት እረኛችን ክርስቶስ እኛን ያገኘባት የምሥጢራቱ መግቢያ ቅድስት ጥምቀት ናት ይሉናል።
☞ ኖላዊ ኄር ዘይቤ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውእቱ (‹‹ቸር ጠባቂ›› ያለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።)
☞ ወአንቀጽኒ ፈለገ ዮርዳኖስ ውእቱ (‹‹በርም›› የዮርዳኖስ ወንዝ(ጥምቀት) ነው።)
☞ ወዐጻዊሰ ዮሐንስ መጥምቅ ውእቱ (‹‹በረኛውም›› ዮሐንስ መጥምቅ ነው፡፡)
☞ ወዐጸድ መንግሥተ ሰማያት ይእቲ ( ‹‹ስፍራም›› መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ )

አበው ሲተርቱ «ባጤ ሞት የተከተረ በስለት የተመተረ አንድ ነው» ይላሉ። ለእኛ የሕይወታችን ዐጤ የነፍሳችን ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ከሥፍራችን እንዳንታጣ ከቤቱ እንዳንወጣ በሞት ሳይሆን በሕይወት እንዲከትረን ከዘልዓለማዊ ዐጸድ ከሰማይ ቤቱ እንዳንጎድልና በፍርዱ ሠይፍ እንዳንመተር ከሥላሴ ልጅነታችን ከተዋህዶ ሃይማኖታችን አያናውጸን።

✍️ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ደቡብ ሱዳን ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን የተጻፈ

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13083

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

China’s stock markets are some of the largest in the world, with total market capitalization reaching RMB 79 trillion (US$12.2 trillion) in 2020. China’s stock markets are seen as a crucial tool for driving economic growth, in particular for financing the country’s rapidly growing high-tech sectors.Although traditionally closed off to overseas investors, China’s financial markets have gradually been loosening restrictions over the past couple of decades. At the same time, reforms have sought to make it easier for Chinese companies to list on onshore stock exchanges, and new programs have been launched in attempts to lure some of China’s most coveted overseas-listed companies back to the country.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from us


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA